ኢፒኦ ሳምንታዊ: ሐምሌ 22-28, 2015
የፖለቲካ እና አጨማሪ መረጃዎች በኢትዮጵያ በአማራ ክልል ከሚፈጥሩ ግጭቶች ሌሎችም ክልሎች ክልል ወደ ግጭት እንደምትገኝ ማግኘት ይችላሉ።
Also available in English
- የፖለቲካ ግጭት ኩነቶች ብዛት: 1,073
- በፖለቲካ ግጭቶች ምክንያት ሪፖርት የተደረጉ የሟቾች ቁጥር: 4,027
- በሰላማዊ ሰዎች ላይ በተሰነዘሩ ጥቃቶች ምክንያት ሪፖርት የተደረጉ የሟቾች ቁጥር: 1,918
- የፖለቲካ ግጭት ኩነቶች ብዛት: 39
- በፖለቲካ ግጭቶች ምክንያት ሪፖርት የተደረጉ የሟቾች ቁጥር: 46
- በሰላማዊ ሰዎች ላይ በተሰነዘሩ ጥቃቶች ምክንያት ሪፖርት የተደረጉ የሟቾች ቁጥር: 9
ኢትዮጵያን በተመለከተ በቁጥር የተደገፉ መረጃዎችን ከኢፒኦ የመረጃ መዝገብ እንዲሁም በዋናው የአክሌድ ኤክስፖርት መሳሪያ ውስጥ ማግኘት ይችላሉ።

የሁኔታዎች አጭር መግለጫ
በፌዴራል መንግስት እና በትግራይ ህዝብ ነፃነት ግንባር በመካከል የተደረገው የሰላም ስምምነት የሰሜን ግጭት እንዲቋጭ ካደረገ በኋላ ባለፈው ሳምንት በአማራ ክልል የፖለቲካ ግጭቶች ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ደርሰዋል።2

ባለፈው ሳምንት አክሌድ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተደረጉ 28 የውጊያ ኩነቶችን የመዘገበ ሲሆን አብዛኛው ውጊያ የተከሰተው በሰሜን ወሎ እና ምዕራብ ጎጃም ዞኖች ነው። የፋኖ ታጣቂዎች አንዳንድ ከተሞችን በመቆጣጠር እስረኞችን ማስፈታት ችለዋል።4 በክልሉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትን እንቅስቃሴ ለመግታት በደብረ ማርቆስ፣ ደምበጫ፣ ቡሬ እና አማኑኤል ከተሞች ሰልፈኞች መንገዶችን በመዝጋታቸው በርካታ ግጭት የተቀላቀለባቸው ስልፎችም ተካሂደዋል።

የሚኖርበት በህዝብ ቁጥር በኢትዮጵያ ሁለተኛ የሆነ ክልል ነው። የአማራ ህዝብ እና በአማራ የተመረጡ ተወካዮች ከ2010 ጀምሮ የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ መንግስት ጠንካራ ደጋፊ ሆነው የቆዩ ሲሆን ከ2013 እስከ 2015 መጀመሪያ ድረስ – የትግራይ መከላከያ ሰራዊት ተብሎም ከሚታወቀው – ከትህነግ/ህወሓት ኃይሎች ጋር በተደረገው ጦርነት ወቅት ጠንካራ መከላከያ ሠራዊት አካል ነበሩ። በዚያን ጊዜ ፋኖ እና ሌሎች የአማራ ብሔር ታጣቂዎች ክልላቸውን ከትህነግ/ህወሀት ኃይሎች ለመከላከል ከኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጎን ተሰልፈው የተዋጉ ሲሆን በምዕራብ ትግራይ ዞን የሚገኙ አካባቢዎችን ጨምሮ ውዝግብ የሚነሳባቸውን ቦታዎች ተቆጣጥረዋል።
ተጨማሪ ንባቦች
- ኢፒኦ ሳምንታዊ: ከሰኔ 24-30, 2015 በአማራ ክልል በአካባቢው የፀጥታ ኃላፊዎች ላይ የሚደርሰው ግድያ መቀጠሉ።
- ኢፒኦ ሳምንታዊ: ከሰኔ 10-16, 2015 በትግራይ ክልል ውዝግብ ባለባቸው ቦታዎች በአማራ ተወላጆች የተደረገ ሰልፍ።