Skip to main content

​​ኢፒኦ ሳምንታዊ :- ከሐምሌ 24, 2013 እስከ ሐምሌ 30, 2013

Summary of weekly conflicts in Ethiopia with focus on Tigray.

12 August 2021

Also available in English

  • የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች – 1,735
  • በተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች ህይወታቸው እንዳለፈ የተዘገቡ ሰዎች – 9,294
  • በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ በተቃጡ ጥቃቶች ህይወታቸው ያለፈ – 4,944

ኢትዮጵያን በተመለከተ በቁጥር የተደገፉ መረጃዎችን እዚህ ሁሉንም የአክሌድ ስራዎች ደግሞ እዚህ ጋር በመጫን ያገኛሉ።

ባለፈው ሳምንት በትግራይ ህዝብ ነፃነት ግንባር እና በመንግሥት ኃይሎች መካከል በአፋር ክልል በፋንቲ ራሱ-ዞን 4፣ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን፣ እና በምዕራብ ትግራይ ዞን ውጊያ ቀጥሏል። ከመንግሥት ጋር ግንኙነት ያላቸው ሀይሎች ትህነግን በመግፋት ቡድኑ ወደ አፋር ክልል የሚያደርገውን ግስጋሴ ላለፉት ሁለት ሳምንታት ማቀዝቀዝ የቻሉ ይመስላል።

በአፋር ክልል የትህነግን እንቅስቃሴ ማቀዝቀዝ የተቻለ ቢሆንም በአማራ ክልል ሰሜናዊ አካባቢዎች የሚዋጉ የትህነግ ታጣቂዎች በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ላሊበላን ጨምሮ አዳዲስ ቦታዎችን መያዝ ችለዋል። ነዋሪዎቹ እንደሚሉት የትህነግ ሃይሎች ወደ ጥንታዊቷ ከተማ ሲገቡ ከመንግሥት ኃይሎች መክላክል አልገጠማቸውም (ሮይተርስ፣ ሐምሌ 30, 2013)። በተጨማሪም ወልዲያ ከተማ፣ ራያ ቆቦ አካባቢ፣ እንዲሁም በሰሜን ወሎ ዞን ጉባ ላፍቶ ወረዳ እና ሀብሮ ወረዳ ዙሪያ በሚገኙ አካባቢዎች ውጊያዎች ተመዝግበዋል። በተጨማሪም በሰሜን ምዕራብ ትግራይ ዞን በአዲ አርቃይ እና ማይ ፀብሪ በመንግስት ሃይሎች እና በትህነግ ታጣቂዎች መካከል ውጊያ ተመዝግበዋል። በእነዚህ ግጭቶች የሞቱት ሰዎች ቁጥር አይታወቅም።

    Country
    Ethiopia
    Share on

    Related content