ኢፒኦ ሳምንታዊ: ከሚያዚያ 15, 2014 እስከ ሚያዚያ 28, 2014
An overview of recent conflicts and events in Ethiopia, with detailed statistics and analysis.
Also available in English
- የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች - 2,912
- በተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች ህይወታቸው እንዳለፈ የተዘገቡ ሰዎች - 15,961
- በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ በተቃጡ ጥቃቶች ህይወታቸው ያለፈ - 7,225
- የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች - 34
- በተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች ህይወታቸው እንዳለፈ የተዘገቡ ሰዎች - 154
- በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ በተቃጡ ጥቃቶች ህይወታቸው ያለፈ - 69

በሚያዚያ ወር ማገባደጃ ላይ በኢትዮጵያ የሚገኙ ሙስሊሞች የኢድ አል ፈጥር በአልን አከብረዋል። ይሁን እንጂ በዓሉ የተከበረው ለብዙ ቀናት በዘለቀ የእርስ በርስ ግጭትና ብጥብጥ መሃል ነው። ሚያዚያ 18 ላይ በጎንደር ከተማ የአንድ ታዋቂ የአካባቢው ሼክ የቀብር ስነ-ስርዓት ላይ ግጭት ከተፈጠረ በኋላ ማንነቱ ያልታወቀ ታጣቂ ቡድን በሙስሊሞች ላይ ጥቃት ሰንዝሯል። በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በነበሩ ሙስሊሞች ላይ ቦምብ ተወርውሮ ሶስት ሰዎች ሲሞቱ አምስት ሰዎች ቆስለዋል። ግጭቱ ወደ ከተማው ተስፋፍቶ የሁከቱ ፈጣሪዎች ከ20 በላይ የሙስሊም ንግድና መኖሪያ ቤቶችን አቃጥለዋል። በተጨማሪም መስጊዶችን አቃጥለው 11 መኖሪያ ቤቶችን ዘርፈዋል (የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ ሚያዚያ 21, 2014)። ይህም ለ17 ሰዎች ሞት ምክንያት ሲሆን ተጨማሪ 118 ሰዎች መቁሰላቸው ተዘግቧል።

ሳምንታዊ ትኩረት፡ በኢትዮጵያ እንደዚህ ያሉትን ግጭቶች አዝማሚያ
የኢትዮጵያ ማህበረሰብ በተለያዩ መስመሮች የተከፋፈለ ሲሆን አሁን ያለው ሁኔታ በብዙ መልኩ ከ2006-2010 ከነበሩት ሰልፎች አንጻር አደገኛ ነው። በኦሮሚያ ክልል በኦነግ-ሸኔ ላይ ለአንድ ወር የተካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ አንዳንድ ለውጦችን ያመጣ ቢመስልም በሁለቱ ወገኖች መካከል እየተካሄደ ያለው ውጊያ በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ባልሆኑ ሰዎች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያደረሰ ነው (ዲደብሊው አማርኛ፣ ሚያዚያ 3, 2014) የግጭት መጠን ሊጨምር ይችላል።