Skip to main content

ኢፒኦ ሳምንታዊ :- ከሚያዚያ 23, 2013 እስከ ሚያዚያ 29, 2013

Ethiopian weekly report detailing political events and humanitarian activities

12 May 2021

Also available in English

በቁጥር (ከመጋቢት 24, 2010 እስከ ሚያዚያ 29, 2013)1

  • የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች – 1,518
  • በተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች ህይወታቸው እንዳለፈ የተዘገቡ ሰዎች – 7,095
  • በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ በተቃጡ ጥቃቶች ህይወታቸው ያለፈ – 3,948

እዚህ፣ሁሉንም የአክሌድ ስራዎች ደግሞ እዚህ ጋር በመጫን ያገኛሉ።

የሁኔታዎች አጭር መግለጫ

ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ካለፉት ሳምንታት በቁጥር ያነሱ የፖለቲካ አለመረጋጋቶች ተመዝግበዋል። የ2013 ጠቅላላ ምርጫ መድረሱን ተከትሎ የፖለቲካው ድባብ ውጥረት ቢነግስበትም ባለፈው ሳምንት በአክሌድ የተመዘገበው የአለመረጋጋት ኩነት አንድ ብቻ ነው፤ ይህም ሰልፍ ላይ የተሳተፉ ግለሰቦች ላይ የተወሰደ አላስፈላጊ ሀይል ነው። 

ሚያዚያ 25, 2013 የአዲስ አበባ ፖሊስ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር የሆኑ ግለሰብ ቤት ውስጥ በሀይል በመግባት ቤቱን የሚጠብቁ የደህንነት ሰራተኞችን አስሮ በቤቱ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ሁሉ ስልኮች እና ላፕቶፖች ወስዷል (ቪኦኤ፣ ሚያዚያ 29, 2013; አዲስ ስታንዳር፣ ሚያዚያ 26, 2013)።. ፖሊስ ይህንን ድርጊት ለመቃወም ከቤቱ ውጪ ተሰብስበው የነበሩ ወጣቶች ላይ ተኩሷል፤ አስሯል (አዲስ ስታንዳርድ፣ ሚያዚያ 26, 2013)።

ሚያዚያ 27, 2013 አካባቢ የፌደራል ሀይሎች የአማራ ወጣቶች ማህበር አባላትን በጅምላ አስረዋል። በተጨማሪም የተወሰኑ የአማራ ክልል ልዩ ሀይል አባላትን ባህር ዳር ውስጥ በነበረው ሰልፍ ወቅት ለነበረው ግጭት ተጠያቂ በማድረግ አስረዋቸዋል (ዲደብሊው አማርኛ፣ ሚያዚያ 26, 2013; ኢፒኦ ሳምንታዊ:- ከሚያዚያ 9, 2013 እስከ 15, 2013)።

የሰብአዊ ድጋፎች እንቅስቃሴ በትግራይ ክልል እና አማራ ክልል

በትግራይ ክልል ምንም እንኳን ሰብአዊ ድጋፍ ለሚያደርጉ ድርጅቶች የተሰጠው ተደራሽነት በከፍተኛ ሁኔታ የተሻሻለ ቢሆንም ባለፈው ሳምንት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰብአዊ ግንኙነቶች ማስተባበሪያ ቢሮ በመአከላዊ፣ ሰሜን ምዕራባዊ፣ ምስራቃዊ፣ ደቡብ ምስራቃዊ፣ እና ደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶች ሰባዊ ድጋፍ የሚያደርጉ ድርጅቶችን ወደ ገጠራማው የትግራይ አካባቢዎች ላይ ከመድረስ አግዷቸዋል ሲል ገልጿል (የተመድ ሰብአዊ ግንኙነቶች ማስተባበሪያ ቢሮ፣ ሚያዚያ 29, 2013)። በተጨማሪም የመገናኛ መስመሮች አለመኖር የቁጥጥር ስራዎችን እና የእርዳታ ማድረስ ጥረቶችን ሂደት ምዘናን እንዲዘገይ አድርጏል። መንግስት የተወሰኑ አካባቢዎች ከወታደራዊ እጀባ ጋር ክፍት መሆናቸውን አስታውቋል (ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ-ኢትዮጵያ፣ ሚያዚያ 30, 2013). ሆኖም መንግስት እነዚህ አካባቢዎች የትኞቹ እንደሆኑ ግልፅ አላደረገም። 

Footnotes

  1. 1

     እነዚህ ቁጥሮች የሚያመለክቱት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደስልጣን ከመጡበት መጋቢት 24, 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በሀገሪቱ የተከሰቱ የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶችን፣ በዚህ ምክንያት የደረሱ የሞት ጉዳቶች፣ እንዲሁም በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ የተቃጡ ጥቃቶችን ነው።

Country
Ethiopia
Region
Africa
Share on

Related content