Skip to main content

ኢፒኦ ሳምንታዊ :- ከሰኔ 26, 2013 እስከ ሐምሌ 2, 2013

Weekly report detailing Ethiopia's political, military situations.

15 July 2021

Also available in English

ኢትዮጵያ በቁጥር (ከመጋቢት 24, 2010 እስከ ሐምሌ 2, 2013)1

  • የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች – 1,630
  • በተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች ህይወታቸው እንዳለፈ የተዘገቡ ሰዎች – 8,373
  • በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ በተቃጡ ጥቃቶች ህይወታቸው ያለፈ – 4,488

ኢትዮጵያን በተመለከተ በቁጥር የተደገፉ መረጃዎችን እዚህ፣ ሁሉንም የአክሌድ ስራዎች ደግሞ እዚህ ጋር በመጫን ያገኛሉ።

የሁኔታዎች አጭር መግለጫ

መንግስት ያሳለፈውን የተኩስ አቁም ውሳኔ እና የክልሉ መዲና መቀሌ በትግራይ ህዝብ ነፃነት ግንባር (ትህነግ/ህወሓት) ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር መውደቅ ተከትሎ በትግራይ ክልል የሚካሄደው ከፍተኛ ውጊያ ባለፈው ሳምንት ረግቧል። ሆኖም ግን የተኩስ አቁም ውሳኔው ተከብሮ ይቆያል ተብሎ አይገመትም።

በሚቀጥሉት ሳምንታት ከባድ ውጊያዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ የሚያመለክቱ ሌሎች አዝማሚያዎች አሉ፡ የመንግሥት የአንድ ወገን የተኩስ አቁም ለሁለቱም ወገኖች የግጭትን የወደፊት እንድምታዎች እንዲገመግሙ በጣም አስፈላጊ ጊዜን ስለሚሰጥ አሁን ያለው ሁኔታ በድርድር የፖለቲካ መፍትሄ የሚደረስበት እና ግጭቱ እስከወዲያኛው የሚቆምበት ይሆናል የሚል ተስፋ አለ፡፡

ከምርጫ ጋር የተያያዙ ክርክሮች ወቅታዊ ሁኔታ

በጠቅላላ ከ46 የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ 31 እና ሰባት የግል እጩዎች ከምርጫ ጋር የተያያዙ ቅሬታዎችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አቅርበዋል።

ምርጫ ቦርድ የምርጫውን ይፋዊ ውጤት ሐምሌ 3, 2013 አስታውቋል፡፡

Footnotes

  1. 1

    እነዚህ ቁጥሮች የሚያመለክቱት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደስልጣን ከመጡበት መጋቢት 24, 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በሀገሪቱ የተከሰቱ የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶችን፣ በዚህ ምክንያት የደረሱ የሞት ጉዳቶች፣ እንዲሁም በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ የተቃጡ ጥቃቶችን ነው።

Country
Ethiopia
Share on

Related content