Update
ኢፒኦ ሳምንታዊ: ከጥር 14, 2014 እስከ ጥር 20, 2014
Weekly reports on political conflicts and actions in Ethiopia's regions.
Also available in English
- የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች – 2,512
- በተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች ህይወታቸው እንዳለፈ የተዘገቡ ሰዎች – 14,363
- በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ በተቃጡ ጥቃቶች ህይወታቸው ያለፈ – 6,495
- የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች – 30
- በተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች ህይወታቸው እንዳለፈ የተዘገቡ ሰዎች – 54
- በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ በተቃጡ ጥቃቶች ህይወታቸው ያለፈ – 9
የሁኔታዎች አጭር መግለጫ
ባሳለፍነው ሳምንት በአፋር ክልል ቂልባቲ ራሱ-ዞን 2 በአባላ፣ በርሀሌ፣ ኢሬብቲ፣ እና መጋሌ አካባቢዎች በትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባር (ትህነግ/ህወሃት) እና በአፋር ክልል ልዩ ሃይሎች እንዲሁም ታጣቂዎች መካከል ውጊያ ተካሂዷል (ከዚህ በታች ያለውን ካርታ ይመልከቱ)። እንደአፋር ክልል መንግስት ገለጻ በዚህ ግጭት ከ220,000 በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ ጥር 18, 2014።


የሁኔታዎች አጭር መግለጫ
በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ፣ ሰሜን ጎንደር፣ እና ሰሜን ወሎ ዞኖች በትህነግ እና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና የአማራ ክልል ልዩ ሃይል መካከል ውጊያዎች መከሰታቸው ታውቋል።
ሳምንታዊ ትኩረት፡ ኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ልታነሳ ስለመሆኑ
ጥር 18 ላይ የኢትዮጵያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥቅምት 23, 2014 የታወጀው የኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲነሳ የሚጠይቅ ውሳኔ ለተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል።



