ኢፒኦ ሳምንታዊ: ከየካቲት 19, 2014 እስከ የካቲት 25, 2014
Overview of recent conflict events and political developments in Ethiopia.
Also available in English
- ኢትዮጵያ በቁጥር (ከመጋቢት 24, 2010 እስከ የካቲት 25, 2014) 1
- የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች – 2,643
- በተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች ህይወታቸው እንዳለፈ የተዘገቡ ሰዎች – 15,063
- በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ በተቃጡ ጥቃቶች ህይወታቸው ያለፈ – 6,958
ኢትዮጵያ በቁጥር (ከየካቲት 19, 2014 እስከ የካቲት 25, 2014) 2
- የተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች – 9
- በተደራጁ የፖለቲካ ግጭቶች ህይወታቸው እንዳለፈ የተዘገቡ ሰዎች – 36
- በግጭት ውስጥ ተሳታፊ ያልሆኑ ግለሰቦች ላይ በተቃጡ ጥቃቶች ህይወታቸው ያለፈ – 6
ኢትዮጵያን በተመለከተ በቁጥር የተደገፉ መረጃዎችን እዚህ፣ ሁሉንም የአክሌድ ስራዎች ደግሞ እዚህ ጋር በመጫን ያገኛሉ።

የሁኔታዎች አጭር መግለጫ
ባለፈው ሳምንት ኢትዮጵያውያን በንጉስ ዳግማዊ ሚኒሊክ የሚመራው የኢትዮጵያ ጦር በጣሊያን ሃይሎች ላይ በ1888 የተጎናጸፈው ድል የሚከበርበትን 126ኛውን የአድዋ ድል አክብረዋል። በአዲስ አበባ የበአሉ ማክበሪያ ቦታ ላይ ለውጥ መደረጉን ተከትሎ በህዝቡ እና የመንግስት ባለስልጣናት መካከል ውጥረት ሰፍኖ ነበር። በዳግማዊ ሚኒሊክ አደባባይ በተከበረው በዓል ላይ አንዳንድ ሰዎች ፀረ-መንግስት መፈክሮችን አሰምተዋል። የካቲት 24 የአድዋ ድል በዓል በተከበረ ማግስት የደቡብ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ፖሊሶች በሀዲያ ዞን ሆሳዕና የሚገኘው ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በመግባት የሚኒሊክን ምስል የያዘ ቲሸርት የለበሱ ተማሪዎችን ደብድበው አቁስለዋል። የጸጥታ ሃይሎቹ ተማሪዎቹን የዳግማዊ ሚኒሊክን ምስል እና አርማ የሌለውን የድሮውን አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ባንዲራ በማድረግ ሁከትና ብጥብጥ በማነሳሳት ከሰዋቸዋል። የድሮውን ባለሶስት ቀለም የኢትዮጵያ ባንዲራ ከመጠቀም ጋር ተያይዞ ግጭት ለመጨረሻ ግዜ የተነሳው በጥር ወር መጀመሪያ በቡራዩ ነበር (ኢፒኦ ሳምንታዊ: ከጥር 7, 2014 እስከ ጥር 13, 2014ን ይመልከቱ)።

ሩሲያ በዩክሬን ላይ በወሰደችው እርምጃ ምክንያት የሚከተለው ኢኮኖሚያዊ መዘዝ በኢትዮጵያ ያለው የማዳበሪያ፣ ነዳጅ፣ እና ጥራጥሬ ዋጋ ላይ መንጸባረቅ ሲጀምር በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የመንግስት ሰዎች ከፍተኛ የግጭት ጫና እና አነስተኛ የመቋቋሚያ ዘዴዎች ሊያጋጥሟቸው ይችላሉ።