Skip to main content

ኢፒኦ ሳምንታዊ ዘገባ (መጋቢት 10, 2016)

የሁኔታዎች አጭር መግለጫ Including conflicts in Amhara and Oromia.

22 March 2024

Also available in English

የሁኔታዎች አጭር መግለጫ

አማራ ክልል ፋኖ ታጣቂዎች እና ኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መካከል የሚደረጉ ውጊያዎች የቀጠሉ ሲሆን የኦሮሞ እና የአማራ ብሔር ታጣቂዎች በሰሜን ሸዋ ዞን ተዋግተዋል። በኦሮሚያ  የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) — በመንግሥት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ)-ሸኔ ተብሎ የሚጠራው ከመንግሥት ኃይሎች ጋር በተለያዩ ቦታዎች ተዋግቷል። ካለፈው ሳምንት ጋር ሲነጻጸር የተመዘገቡ የፖለቲካ ግጭቶች በመላ አገሪቱ 50% በላይ ቀንሰዋል።

ብሔር ተኮር ውጊያዎች በአማራ ክልል

በአማራ ክልል በፋኖ ታጣቂዎች እና በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መካከል የሚደረጉ ውጊያዎች በሰሜን ወሎ እና ምዕራብ ጎጃም ዞኖች መከሰታቸው የተዘገበ ሲሆን ይኸም ባለፈው ሳምንት በክልሉ ያለው ግጭት በመጠኑ መቀነሱን ያሳያል። ከየካቲት ወር አጋማሽ ጀምሮ በክልሉ በፋኖ እና በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መካከል የሚደረገው ውጊያ ወደ ከተሞች በመዛመቱን ተከትሎ በክልሉ ያለው ውጊያ ተባብሶ ነበር

የፋኖ ታጣቂዎች እና የፌደራል መንግስትን ወደ ሰላም ድርድር ለማምጣት ያልተቋረጠ ጥረት እየተደረገ አይደለም። ሆኖም በመጋቢት 3 ቀን የኢትዮጵያ የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ መንግስትጥያቄ አለኝ ከሚል ቡድን ጋር ለመደራደርዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።1ቦርከና፣የኢትዮጵያ መንግስትከየትኛውም ቡድን ጋር በማንኛውም ጥያቄ ለመደራደር ዝግጁ ነኝ አለመጋቢት 3, 2016 መንግስት ለድርድር መዘጋጀቱን የተገለጸ ቢሆንም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቃዋሚ የምክር ቤት አባልና የመንግሥት ወጪና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የነበሩትን የክርስቲያን ታደለን ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ድምፅ ሰጥቷል።2 ክርስቲያን ታደለ በአማራ ክልል ከፋኖ ታጣቂዎች ጋር የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ በኋላ በነሐሴ 2015 በቁጥጥር ስር ውለዋል። በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በጥር ወር ታሰረው የነበሩት ሌላው የተቃዋሚ የፓርላማ አባል ደሳለኝ ጫኔ መጋቢት 5 ቀን ከእስር ተፈትተዋል።3

በኦሮሚያ ክልል ውጊያ እና በሰላማዊ ሰዎች ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት

በኦሮሚያ ክልልም በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እና በኦነሠ/ኦነግሸኔ ታጣቂዎች መካከል የሚደረገው ውጊያ ቀጥሏል። በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉደቱ ቆንዶሌ ወረዳ እና በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አባቦ ወረዳ በቡድኑ ላይ ዘመቻ እየተደረገ እንደሆነ የመንግስት ምንጮች አስታውቀዋል። በተመሳሳይ በአርሲ እና በሰሜን ሸዋ ዞኖች ተጨማሪ ውጊያዎች መከሰታቸውም ተዘግቧል።

በተጨማሪም በአርሲ ዞን ከደራ ከተማ ወጣ ብሎ የሚገኘው የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ አምስት ሠራተኞች ከሁለት ሳምንት በፊት ታግተው ከተወሰዱ በኃላ ባለፈው ሳምንት ተገድለው ተገኝተዋል። በኦሮሚያ ክልል በውጊያዎች መስፋፋት ምክንያት እገታዎች ከባለፈው አንድ ዓመት ጀምሮ ጨምረዋል

መፈናቀል በትግራይ ክልል

መጋቢት 3 ቀን ከምዕራብ ትግራይ ዞን ከሁመራና አካባቢዋ መንደሮች የተፈናቀሉ ተጨማሪ 28 የትግራይ ተወላጆች በሰሜን ምዕራብ ትግራይ ዞን በምትገኘው ሽሬ ከተማ ደርሰዋል።4 የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ከተቀሰቀሰበት ከጥቅምት 2013 ጀምሮ የአማራ ኃይሎች የምዕራብ ትግራይ ዞን ተቆጣጥረውታል። በ2013 ግጭቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከተፈናቀሉት በሺዎች ከሚቆጠሩት ሰዎች ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ቁጥር ያለው ቢሆንም ከእነዚህ የይገባኛል ጥያቄ ከሚነሳባቸው አካባቢዎች የተፈናቀሉት የትግራይ ተወላጆች ጉዳይ ጉልህ ነው (የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው አካባቢዎች ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ኢፒኦ ወርሃዊ፡ ከጥር 23 እስከ የካቲት 21, 2016ን ይመልከቱ)። 

መጋቢት 2 ቀን የትግራይ ጊዜያዊ ክልላዊ አስተዳደር እና የትግራይ ህዝብ ነፃነት ግንባር (ትህነግ/ህወሓት) ከፌዴራል መንግስት ባለስልጣናት ጋር በአፍሪካ ህብረት በመታገዝ በኢትዮጵያ የዘለቂ የጦርነት ማቆም ስምምነት አፈፃፀም ላይ ተወያይተዋል።5 ይህ ስምምነት በጥቅምት 2015 በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን አስከፊ ግጭት ለማስቆም በትህነግ/ህወሓት እና በመንግስት ተፈርሟል። የአውሮፓ ህብረት እና የቡድን 7 ሀገራት በመጋቢት 4 ቀን መግለጫ አውጥተው ስብሰባውን በአሉታዊ ተቀብለው የተፋላሚዎችን ትጥቅ ለማስፈታት እና አደረጃጀታቸውን ለማፍረስ እንዲሁም በግጭቱ የተጎዱ ወገኖችን ችግር ለመፍታት ተጨማሪ መሻሻል እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።6

Related content