ኢፒኦ ሳምንታዊ ዘገባ (ጥር 28, 2016)
Summary of events and conflicts in Ethiopia, particularly in Amhara and Oromia regions.
Also available in English
የሁኔታዎች አጭር መግለጫ
ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ በአማራ ክልል በፋኖ ታጣቂዎች እና በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መካከል ከሚደረጉ ውጊያዎች ጋር በተያያዘ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የደረሱ ጥቃቶች ተዘግበዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በኦሮሚያ ክልል በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት(ኦነሠ) — በመንግሥት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ)-ሸኔ ተብሎ በሚጠራው — የታወጀው የትራንስፖርት አድማ ውጊያዎች እና በሰላምዊ ሰዎች ላይ ተጨማሪ ጥቃት እንዲፈፀም ምክንያት ሆኗል። በትግራይ ክልልም የተቃውሞ ሰልፎች ቀጥለዋል።
በአማራ ክልል በሰላማዊ ሰዎች ላይ የደረሱ ጥቃቶች
ውጊያዎች በአማራ ክልል የቀጠሉ ሲሆን በፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች መካከል በደቡብ ወሎ እና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ውጊያዎች ተከስተዋል። በመርዓዊ ከተማ ከባድ ውጊያ መደረጉ የተዘገበ ሲሆን በውጊያው ሁለት የኦርቶዶክስ አብያተ ክርሰትያናት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ተዋጊዎች ተገድለዋል። ውጊያውን ተከትሎ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ኃይሎች ከአማራ ክልል ፖሊስ እና ከቀበሌ ታጣቂዎች ጋር በመተባበር ቢያንስ 50 ሰላማዊ ሰዎችን ተኩሰው ገድለዋል።
