ኢፒኦ ወርሀዊ: ሐምሌ 25 እስከ ነሐሴ 25, 2014
A report summarizing political turmoil and human rights issues in northern Ethiopia from July 25 to August 25, 2014.
Also available in English
ከሐምሌ 25 እስከ ነሐሴ 25, 2014 በጨረፍታ
አበይት አሃዝ
- አክሌድ ከሐምሌ 25 እስከ ነሐሴ 25, 2014 ዓ.ም ድረስ 113 የተደራጁ የፖለቲካ ግጭት ኩነቶችን እና 558 ሪፖርት የተደረጉ ሟቾችን መዝግቧል።
- በተደራጀ የፖለቲካ ግጭት ምክንያት ከፍተኛው ሪፖርት የተደረጉ የሟቾች ቁጥር በኦሮሚያ ክልል የተመዘገበ ሲሆን 387 ሪፖርት የተደረጉ ሟቾች ተመዝግበዋል። የአማራ ክልል በ95 ሪፖርት የተደረጉ ሟቾች ቁጥር በሁለተኝነት ይከተላል።
- ከሐምሌ 25 እስከ ነሐሴ 25, 2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ተደጋግሞ የተከሰተው የኩነት አይነት ጦርነት ሲሆን 66 ኩነቶች ከ274 ሪፖርት የተደረጉ የሟቾች ቁጥር ጋር ተመዝግበዋል። በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶች በ40 ኩነቶች እና 257 ሪፖርት የተደረጉ ሟቾች ቁጥር በሁለተኝነት ይከተላል።
አበይት ክንውኖች
- በአማራ፣ ትግራይ እና አፋር ክልሎች ነሐሴ 18 ቀን በመንግስት ኃይሎች እና በትግራይ ህዝብ ነፃነት ግንባር (ትህነግ/ህወሓት) መካከል ሌላ ዙር ውጊያ ተጀምሯል።
- ከሐምሌ 25 እስከ ነሐሴ 25, 2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በኦሮሚያ ክልል የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ)-ሸኔ እና የመንግስት ኃይሎች ማለትም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እና የኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይል መዋጋት ቀጥለዋል።
- በኦሮሚያ ክልል በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚደርሰው ጥቃት የቀጠለ ሲሆን በሰላማዊ ሰዎች ላይ በደረሰ ጥቃት ምክንያት የሞቱ ሰዎች ከፍተኛው ቁጥር በሆሮ ጉዱሩ ዞን በአምሩ ወረዳ ተመዝግቧል።
- ከሐምሌ 25 እስከ ነሐሴ 25, 2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በአፋር ክልል በጋቢ-ዞን 3 በገዳማይቱ፣ በዳንላህላይ እና በሶማሌ ክልል በሲቲ ዞን በሚኤሶ ወረዳ በሚገኙ ሌሎች አወዛጋቢ አካባቢዎች በሶማሌ እና በአፋር ብሔረሰብ ታጣቂዎች መካከል ውጊያ ተቀስቅሷል።

ከሐምሌ 25 እስከ ነሐሴ 25, 2014 የሁኔታዎች አጭር መግለጫ
ከአምስት ወራት አንፃራዊ መረጋጋት በኋላ ነሐሴ 18 ቀን የሰሜን ኢትዮጵያ ውጊያ እንደገና ተቀስቅሷል። በዚህ ምክንያት ከሐምሌ 25 እስከ ነሐሴ 25, 2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በሰሜን አብዛኛው የውጊያ ኩነቶች የተመዘገቡት በአማራ እና በትግራይ ክልሎች መካከል ነው። በኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በቤንሻንጉል/ጉሙዝ እና በሶማሌ ክልሎችም የተከሰቱት ጦርነቶች ተመዝግበዋል። ውጊያው የተጀመረው በትግራይ ክልል በደቡብ ትግራይ ዞን እና በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን አዋሳኝ አካባቢዎች ነው። ነሐሴ 18 ቀን የትህነግ/ህወሓት ኃይሎች በአፋር ክልል ፋንቲ ራሱ-ዞን 2 በያሎ ወረዳ በሚገኙ ሶስት ቀበሌዎችን በከባድ መሳሪያ በመደብዳባቸው ሦስት ሰላማዊ ሰዎች ሞተዋል። በወሩ መገባደጃ ላይ በትህነግ/ህወሓት ኃይሎች እና በመንግስት ኃይሎች መካከል ውጊያዎች በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ዞን እና በትግራይ ክልል ምዕራብ ትግራይ እና ሰሜን ምዕራብ ትግራይ ዞን ተዛምቷል (በሰሜን ኢትዮጵያ ውጊያ የተከሰተባቸው ቦታዎች ዝርዝር ለማየት ኢፒኦ ሳምንታዊ: ነሐሴ 7-ጷጉሜ 4, 2014 ይመልከቱ)። ከነሐሴ 18 እስከ 25 ደረስ በአፋር፣ በአማራ እና በትግራይ ክልሎች 37 የጦርነት ኩነቶች ተመዝግበዋል። ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ – 25 የጦርነት ኩነቶች – በአማራ ክልል የተመዘገቡ ሲሆን በትግራይ ክልል 11 የጦርነት ኩነቶች ተመዝግበዋል።

ወርሃዊ ትኩረት፡ የሰብአዊ ፍላጎቶች በሰሜን ኢትዮጵያ
በግጭቶችም ሆነ በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት በኢትዮጵያ የሰብአዊ ፍላጎቶች አሁንም በከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት (ዩኤንኦሲኤችኤ) እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ በግጭቶች እና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የሰብአዊ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል (ኦሲኤችኤ፣ ነሐሴ 27, 2014)። አፋር፣ አማራ፣ ቤንሻንጉል/ጉሙዝ፣ ኦሮሚያ እና ትግራይ ክልሎች በግጭት ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ክልሎች ሲሆኑ አፋር፣ ጋምቤላ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች እና ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች በአብዛኛው እንደ ድርቅ እና ጎርፍ ባሉ የተፈጥሮ አደጋዎች የተጠቁ ናቸው። ኢትዮጵያ አጠቃላይ የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ከ2020 መገባደጃ ጀምሮ አራት ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች ዝናብ ባለመዝነቡ 40 ዓመታት ታይቶ የማይታወቅ የድርቅ አደጋ ታይቷል። በድርቁ ምክንያት በአፍሪካ ቀንድ 22 ሚሊዮን ሰዎች ላይ የረሃብ አደጋ እንደተጋረጠ ይገመታል (ዘ ጋርዲያን፣ ነሐሴ 14, 2014)። በኢትዮጵያ በድርቅ በጣም የተጠቁ አፋር፣ ኦሮሚያ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች እና ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች – ወይም በአፍሪካ ቀንድ ከተጎጂው ህዝብ 45 በመቶው – ለከፋ ረሃብ የተጋለጡ ናቸው (ዲደብሊው፣ ነሐሴ 10, 2014)። በአዎንታዊ ዜና ባለፈው ሳምንት 23,000 ሜትሪክ ቶን የዩክሬን እህል ኢትዮጵያ ገብቷል (ቢቢሲ አማርኛ፣ ጳጉሜ 2, 2014፤ ኤፒ ኒውስ፣ ነሐሴ 9, 2014)።