ኢትዮጵያ ሳምንታዊ ዘገባ (ነሐሴ 7, 2016)
በትግራይ ክልል የተፈጠረ ልዩነት ባለፈው ሳምንት የተጨመረ ሲሆን በአማራ ክልል ውጊያዎች እና ጥቃቶች ተመዝግበዋል።
Also available in English
የሁኔታዎች አጭር መግለጫ
በትግራይ ህዝብ ነፃነት ግንባር (ትህነግ/ህወሓት) ከፍተኛ አመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት ባለፈው ሳምንት የበለጠ የሰፋ ሲሆን ይኽውም በትግራይ ክልል ተጨማሪ አለመረጋጋት እንዳይፈጥር ስጋት ደቅኗል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በአማራ ክልል ውጊያዎች እና ሰላማዊ ሰዎችን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች መከሰታቸው ተዘግቧል።
ትህነግ/ህወሓት ወደ ቀድሞ ፓርቲነት እንደገና ለመመለስ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ ተደረገ
ነሐሴ 3 ቀን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትህነግ/ህወሓት ወደ ቀድሞ ፓርቲነቱ ለመመለስ ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ ያደረገ ሲሆን በምትኩ ፓርቲውን ‘በልዩ ሁኔታ’ ስር መዝግቦታል。
1 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መሠረት ፓርቲው በግጭት ውስጥ በመሳተፋቸው ምክንያት የተሰረዙ ፓርቲዎችን ወደ ቀድሞ ፓርቲናታቸው ለመመለስ የህግ ገደብ በመኖሩ ወደ ነበሩበት መመለስ አይቻልም。2 ፓርቲው ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በፊት ወደ ነበረበት ደረጃ ለመመለስ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ በመደረጉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትህነግ/ህወሓት የምዝገባ ሂደቱን ለማጠናቀቅ በቀጣይ ስድስት ወራት ውስጥ የጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ፣ አዲስ አምራር እንዲመርጥ እና የፓርቲውን መመሥረቻ ህግ እንዲያፀድቅ ጠይቆታል。3 በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቦርድ አባላት ተሳትፎውን እና ጉባኤው ውዝግብዎችን ጠብቆ መካሄዱን ለማረጋገጥ ፓርቲው ከጠቅላላ ጉባኤ 21 ቀናትን አስቀድሞ ሊያሳውቀው እንደሚገባ አሳስቧል።
ውጊያዎች እና ሰላማዊ ሰዎችን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች በአማራ ክልል
በአማራ ክልል በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚደረጉ ውጊያዎች የቀጠሉ ሲሆን በአውይ፣ በምስራቅ ጎጃም፣ ምዕራብ ጎጃም፣ ሰሜን ሸዋ፣ ሰሜን ወሎ እና ደቡብ ጎንደር ዞኖች ውስጥ ውጊያዎች መደረጋቸው ተዘግቧል። በደቡብ ጎንደር ዞን ውስጥ ትልቅ ከተማ በሆነቸው እና በቢ22 አውራጎዳና ላይ በሚትገኘው በደብረ ታቦር ከተማ ከሐምሌ 27 እስከ 30 ድረስ የዘለቀ የሶስት ቀናት ውጊያ ተደርጓል።
አክሌድ ሰላማዊ ሰዎችን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶችንም መዝግቧል። ባለፈው ሳምንት ለገንዘብ ሲባል የታገተ የሰብዓዊ ድጋፍ ሠራተኛ ቆየት ብሎ ማንነታቸው ባልተገለፀ ታጠቂ ቡድን በሰሜን ወሎ ዞን ዳውንት ወረዳ ውስጥ ተገድሏል።10 ሐምሌ 27 ቀን የታጠቁ ሰዎች በምዕራብ ጎንደር ዞን አውላላ አኩሻራ ካምፕ አቅራቢያ ተኩስ በመክፈት የሱዳን ስደተኞችን አቁስለዋል። በክልሉ ማንነታቸው ያልተገለፀ ታጣቂዎች ስደተኞችን ኢላማ ማድረጋቸው እየጨመረ የመጣ ችግር ሆኗል። የፀጥታ ችግሩን በመቃወም በግንቦት ወር ውስጥ በሺህዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ካምፑን ለቀው ወጥተዋል።

ኢትዮጵያ በጨረፍታ
ሐምሌ 27-ነሐሴ 3, 2016
ይህ መረጃ/ዳታ ሐምሌ 27 እስከ ነሐሴ 3, 2016 ያለውን ጊዜ ይሸፈናል። አክሌድ መረጃን እንዴት እንደሚሰበስብ እና ኩነቶችን እንዴት እንደሚመድብ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የአክሌድን የኮድ መጽሐፍን ይመልከቱ። በዚህ የጊዜ ገደብ ውስጥ የተከሰቱ አንዳንድ ኩነቶች በዘገባ መዘግየት ምክንያት በሚቀጥሉት ሳምንታት ዳታ ውስጥ ሊካተቱ ይችላሉ።
- የኩነት አይነቶች
- ውጊያዎች: 60 ኩነቶች
- ፍንዳታዎች/ የርቀት ግጭት: 0 ኩነት
- ሰላማዊ ሰዎች ላይ የደረሱ ጥቃቶች: 9 ኩነቶች
- የአመፅ ግጭት: 0 ኩነት
- ሰልፎች: 0 ኩነት
- ግጭት ያለበት የተቃውሞ ሰልፍ: 0 ኩነት
Footnotes
- 1
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ‘የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) የሕግ ሰውነት ጉዳይን በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ፣’ ነሐሴ 3, 2016
- 2
ሲሳይ ሳህሉ፣ ‘ሕወሓት ወደነበረበት ሕጋዊ ሰውነት ለመመለስ ያቀረበው ጥያቄ ቀርቶ በልዩ ሁኔታ ተመዘገበ፣’ ሪፖርተር፣ ነሐሴ 5, 2016
- 3
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ‘የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) የሕግ ሰውነት ጉዳይን በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ፣’ ነሐሴ 3, 2016
- 10
ሪሊፍ ዌብ፣ ‘በአማራ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ ሠራተኛ ግድያን በማስመልከት የተሰጠ መግለጫ፣’ ነሐሴ 8, 2016
- 11
ይህ ውጊያዎችን፣ ፍንዳታዎች/ የርቀት ግጭት እና ሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን የሚመለከቱ ኩነቶችን እንዲሁም የአመፅ ግጭት ንዑስ ኩነት የሆነውን የአመፅ ኩነትን ይጨምራል.
- 12
ይህ የተቃውሞ ሰልፎች የኩነት አይነትን እንዲሁም የአመፅ ግጭት ንዑስ ኩነት የሆነውን ግጭት ያለበት የተቃውሞ ሰልፍ ኩነትን ይጨምራል.