ኢትዮጵያ ሳምንታዊ ዘገባ (ታኅሣሥ 1, 2017)
Summary of events and conflicts in Oromia and Amhara regions within Ethiopia updated weekly.
Also available in English
የሁኔታዎች አጭር መግለጫ
ከመንግሥት ጋር የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በመቶዎች የሚቆጠሩ በሰኚ ነጋሳ የሚመራ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት (ኦነሠ) — በመንግሥት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)-ሸኔ ተብሎ የሚጠራው — ቡድን ተዋጊዎች በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የተሃድሶ ጣቢያ ገብተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በአማራ ክልል በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚደረጉ ውጊያዎች በሸዋ ሮቢት፣ በደላንታ እና በደጋ ዳሞት ወረዳዎች ተባብሰዋል።
በኦሮሚያ ክልል ተዋጊዎች የተሃድሶ ጣቢያዎች ገቡ
ኅዳር 22 ቀን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት እና የኦነሠ/ኦነግ-ሸኔ የቀድሞ የማዕከላዊ ዞን አዛዥ ሰኚ ነጋሳ ቡድን መካከል የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ ባለፈው ሳምንት በመቶዎች የሚቆጠሩ ተዋጊዎች የመንግሥት የተሃድሶ ጣቢያ ገብተዋል። በስምምነቱ መሠረት ታጣቂዎቹን ከህብረተሰቡ ጋር መልሶ ለማዋሀድ በመንግሥት የሚተዳደሩ ካምፖች ተዘጋጅተዋል። በመንግሥት ምንጮች መሠረት በአብዛኛው ከምዕራብ እና ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞኖች የተወጣጡ የኦነሠ/ኦነግ-ሸኔ ተዋጊዎች1
ᷲᷟ᷾᷼
᷿ᷰᷲᷱ᷾᷶
é#233;
᷺᷵᷵